.

.
ዋና ገጽ » » "ጥያቄአለኝ?". ምኔ ነዉ ክርስቲ ያን?

"ጥያቄአለኝ?". ምኔ ነዉ ክርስቲ ያን?

ዲያቆን ንጋቱ አበበUnknown ቤተልሔም ዘተዋሕዶ Tuesday, February 17, 2015 | 11:02 PM





¤በአንገቴ ላይ መስቀሉን ከማህተቡ ጋር አስሬ ክርስቶስን እየሰበኩ ምግባሬ እምነቴን ካልገለፀዉ ምኔ ነዉክርስቲያን?
¤
ክርስቲያን ተብዬ ድራፍት ቤቱን ያጨናነኩት ረቡእ አርብን ሽሬ ስጋ እያማረጥኩ ከተሰለፍኩ ምኔ ነዉክርስቲያን?


¤
በየመጠጥ ቤቱ በየጭፈራዉ ቦታ 'እሱ ጣጣም የለው...' ተብዬ የምገኘዉ ማህተቤን አሰዳቢ ከሆንኩ ምኔነዉ ክርስቲያን??
¤
ኦርቶዶክስ እኮ እስክባል ከጫቱ ቅጠል፣ ከትንባሆዉ ጢስ ካልራኩ የድፍረቴ ጥጉ መብቴ እስኪ መስለኝ/ በር ድረስ እያጨስኩ ስደርስ ብቻ ረግጬዉ ከገባው ምኔ ነዉ ክርስቲያን??
¤
የከተራዉ የደመራዉ የበአላቱ ቀንነጠላዬን ለብሼ፣/እሱንም በሰበብስለ ታቦት ብጠየቅ ስለ መስቀልስጠየቅ መልስ ካልሰጠዉ?
¤
የፀሎት መፀሃፍ በአይነቱ መፀሃፍ ቅዱስ በብዛት ደርድሬ ለመግለጥ ግን ከሰነፍኩ..
¤
አስቀዳሽ ጿሚ ተብዬ ቅዱስ ስጋዉን ክቡር ደሙን ተቀብዬ ቤቴ ስገባ አንደበቴን ለስድብ ከከፈትኩ ምኔነዉ ክርስቲያን??
¤
በቅዱስ ቃሉ ማህተብ በስርአተ-ተክሊል ትዳር መስርቼ ሚስቴን ከሰደብኩ፣ከመታው፣ከፈታሁ ምኔ ነዉክርስቲያን?
¤
ድንግል እናቴን አማላጅ ብዬ ካሉኝ ሁሉ ቀናት ሰንበትን መስጠት አቅቶኝ የእመብርሃንን ታምሯንካልሰማዉ ምኔ ነዉ ክርስቲያን?
¤ 
በሃይማኖታዊ በአላት ቅዱሳን በሚከብሩበት ቀን በአለም ሞቅታ ተስቤ ለፆም መያዣ/መፍቻ በሚልሰበብ ከሰከርኩ፤ከዘሞትኩ ምኔ ነዉ ክርስቲያን?
¤
የዝማሬዉ ካሴት ከአለሙ ዘፈን ጋር ደርድሬ ለምርጫ ስቸገር የቅዱሳኑን ስእል ከአለም ሰዎች ጋር ለጥፌለመስገድ ስጨነቅ ምኔ ነዉ ክርስቲያን??
¤
አገልጋይ ተብዬ ///ቤት ገብቼ በሰከረ አንደበት ለምስጋና ስነሳሳበ በወንዴም በእህቴ ላይ ቂም ይዤከወረብኩ ምኔ ነዉ ክርስቲያን??
¤
ነጠላ ለብሼ ለመማር ወጥቼ ከሴት/ከወንድ ጋር የቅድስትቤ/ አጥር ተደግፌ በሴሰነኝነት ከታወርኩ ምኔነዉ ክርስቲያን??
¤
እንከን የሌለባት አባቶቼ በጸናት ያቆይዋትቅድስት / ያስተማረችኝን ካልኖርኩበት ኦርቶዶክስ እኮ ተብዬስሟን ካጎደደፍኩ ምኔ ነዉ ክርስቲያን?

0 comments:

Post a Comment

በሳምንት ጊዜ ውስጥ ብዙ የተነበቡ